የሥጋት አስተዳደር እና ተገዢነት ስልጠና አሰልጣኝ/አማካሪ ግዥ ጨረታ
አቅራቢ ድርጅት፦ ቪዥን ፈንድ ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም አ.ማ (Vision Fund MFI)
ቪዥን ፈንድ ማይክሮ ፋይናንስ ተቋም ለሠራተኞቹ በ “Risk & Compliance” ዘርፍ ስልጠና መስጠት የሚችሉ ብቁ አማካሪዎችን/አሰልጣኞችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።
1. የአገልግሎቱ ዝርዝር
2. ተጫራቾች ማሟላት ያለባቸው መስፈርቶች
-
ሕጋዊ ሰነዶች፦ የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ የቲን (TIN) ሰርተፍኬት፣ የቫት (VAT) ምዝገባ፣ የግብር ክሊራንስ እና የ “PPA” ምዝገባ ምስክር ወረቀት።
-
የጨረታ ማስከበሪያ (CPO)፦ ብር 20,000.00 (ሃያ ሺህ ብር) በሲፒኦ (CPO) ወይም በሁኔታዎች ላይ ያልተመሠረተ የባንክ ዋስትና (ቢያንስ ለ 90 ቀናት የሚቆይ)።
3. የጨረታ ሰነድ አወሳሰድ እና ክፍያ
-
የሰነድ ዋጋ፦ የማይመለስ ብር 300.00 (ሦስት መቶ ብር)።
-
ክፍያ፦ በአዋሽ ባንክ ገረጂ ቅርንጫፍ በቪዥን ፈንድ የሂሳብ ቁጥር 01302059653300 ገቢ በማድረግ የክፍያ ደረሰኙን ማቅረብ።
-
የሰነድ መገኛ፦ ቦሌ ክፍለ ከተማ፣ ወረዳ 06፣ ገረጂ መብራት ኃይል አካባቢ በሚገኘው የቪዥን ፈንድ ዋና መሥሪያ ቤት (Supply Chain and Logistics Department)።
4. የጨረታ መዝጊያ እና አቀራረብ
-
አቀራረብ፦ ቴክኒካል እና ፋይናንሻል ሰነዶች ኦሪጅናል እና ኮፒ ተለይተው በታሸገ ፖስታ መቅረብ አለባቸው።
-
የመዝጊያ ቀን፦ ሚያዝያ 24 ቀን 2018 ዓ.ም (May 02, 2026) ከቀኑ 10:30 (4:30 PM) ሰዓት።
-
የመክፈቻ ጊዜ፦ ሚያዝያ 28 ቀን 2018 ዓ.ም (May 06, 2026) ጠዋት 4:00 (10:00 AM) በቪዥን ፈንድ ዋና መሥሪያ ቤት 4ኛ ፎቅ የመሰብሰቢያ አዳራሽ።
5. አድራሻ እና መገናኛ