የኢአርፒ (ERP) ሲስተም ፍላጎት ጥናትና ስትራቴጂ ነደፋ የማማከር አገልግሎት ጨረታ
ኤም ኤስ አይ ኢትዮጵያ (MSI Ethiopia Reproductive Choices)
ኤም ኤስ አይ ኢትዮጵያ (MSI Ethiopia) የድርጅቱን የሥራ እንቅስቃሴ ዘመናዊ ለማድረግ የሚያስችል የኢንተርፕራይዝ ሪሶርስ ፕላኒንግ (ERP) ሲስተም ለመዘርጋት የሚያስችል ሁለንተናዊ የፍላጎት ጥናት (Needs Assessment)፣ ስትራቴጂ እና የአተገባበር ፍኖተ-ካርታ የሚያዘጋጅ አማካሪ ድርጅት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።
1. የአማካሪው ዋና ዋና የሥራ ድርሻዎች
-
የድርጅቱን ዝርዝር የኢአርፒ (ERP) ፍላጎት ማጥናት።
-
ተግባራዊና ቴክኒካዊ መስፈርቶችን (Functional and Technical Requirements) መለየት።
-
የሲስተም አማራጮችን መገምገም (በራስ መሥራት ወይስ ከውጭ መግዛት)።
-
ለሲስተም አቅራቢዎች የሚቀርብ የቴክኒክ የጨረታ ሰነድ (RFP) ማዘጋጀት።
-
ብቃት ያላቸውን የኢአርፒ ሲስተም አቅራቢዎችን/አስፈጻሚዎችን መለየትና መምከር።
2. ተጫራቾች ማሟላት ያለባቸው መስፈርቶች
-
ሕጋዊ ሰነዶች፦ የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ የቲን (TIN) ሰርተፊኬት እና የቫት (VAT) ምዝገባ ሰርተፍኬት።
-
የሰነድ አቀራረብ፦ የቴክኒክ እና የፋይናንሻል ፕሮፖዛል በሁለት ለየብቻ በታሸጉ ፖስታዎች መቅረብ አለባቸው።
-
ማሳሰቢያ፦ ሁሉም የጨረታ ሰነዶች የተፈረሙና የድርጅቱ ማኅተም ያረፈባቸው መሆን ይኖርባቸዋል።
3. የጨረታ ሰነድ አወሳሰድ እና መዝጊያ ቀን
-
የሰነድ መገኛ፦ ወሎ ሰፈር፣ ተባበር በርታ ሕንፃ ፊት ለፊት በሚገኘው የኤም ኤስ አይ ኢትዮጵያ ዋና መሥሪያ ቤት (Support Office)።
-
የመጀመሪያ ቀን፦ መጋቢት 21 ቀን 2018 ዓ.ም (March 30, 2026) ጀምሮ።
-
የመዝጊያ ቀን፦ ሚያዝያ 06 ቀን 2018 ዓ.ም (April 14, 2026) እስከ ጠዋት 4:00 (10:00 AM) ሰዓት።
-
የመክፈቻ ጊዜ፦ በዕለቱ ሚያዝያ 06 ቀን 2018 ዓ.ም ጠዋት 4:30 (10:30 AM) በድርጅቱ የስብሰባ አዳራሽ ተጫራቾች ወይም ወኪሎቻቸው በተገኙበት።
4. አድራሻ እና መገናኛ