You have no bookmark.
ቦታ: አዲስ አበባ ከተማ፣ ቂርቆስ ክ/ከተማ፣ ለገሀር በሚገኘው የአቢሲንያ ባንክ አ.ማ ዋና መስሪያ ቤት 4ኛ ፎቅ ላይ በሚገኘው አዳራሽ ውስጥ።
የጨረታ ማስከበሪያ (CPO):
ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ንብረት የጨረታ መነሻ ዋጋ ¼ (አንድ አራተኛ) በባንክ በተረጋገጠ ቼክ ወይም ሲ.ፒ.ኦ በአቢሲንያ ባንክ (አ.ማ) ስም በማሰራት ማስያዝ አለባቸው።
የክፍያ ግዴታ እና ቅጣት:
የጨረታው አሸናፊ አሸናፊነቱ ከባንኩ በደብዳቤ ከተገለጸለት ቀን ጀምሮ በ15 (አሥራ አምስት) ቀናት ውስጥ ጠቅላላ ዋጋውን አጠቃሎ መክፈል አለበት።
በዚህ ጊዜ ውስጥ ካልከፈለ፣ ጨረታው ተሰርዞ ያስያዘው ሲ.ፒ.ኦ ለባንኩ ገቢ ይሆናል።
በጨረታው ለተሸነፉት ተጫራቾች ያስያዙት ሲ.ፒ.ኦ ይመለስላቸዋል።
የወጪ ክፍያ:
የጨረታው አሸናፊ ከሚገዛው ንብረት ጋር የተያያዙ ማናቸውንም ለመንግስት የሚከፈሉ ክፍያዎች፣ ግብር፣ 15% የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) እንዲሁም ከስም ዝውውር ጋር የሚገናኙ ማናቸውንም ወጪዎች ይከፍላል።
ውዝፍ የሊዝ ክፍያ ካለ ባንኩ የሚከፍል ሲሆን ለቀሪው የሊዝ ክፍያ ገዢው ከሚመለከተው የመንግስት አካል ጋር ይዋዋላል።
ብድር ማመቻቸት:
ባንኩ የብድር ፖሊሲና መመሪያ መሰረት መስፈርቱን ለሚያሟላ የጨረታው ከፍተኛ ዋጋ አቅራቢ/አሸናፊ ከፊል ብድር ሊሰጥ ይችላል።
መያዣ ሰጪው: ተበዳሪው/መያዣ ሰጪው በሐራጁ ቀንና ሰዓት በቦታው መገኘት ይችላሉ። ባይገኙ ግን ሐራጁ በሌሉበት ይካሄዳል።
ንብረት መጎብኘት: ንብረቶቹን በሥራ ሰዓት ፕሮግራም አስይዞ መጎብኘት ወይም ማየት ይቻላል።
ስልክ ቁጥር: 0115 15 11 53 እና 0115 15 07 11
No products in the cart.
Account details will be confirmed via email.
For faster login or register use your social account.