You have no bookmark.
የጨረታ ማስከበሪያ (CPO):
ተጫራቾች የጨረታውን መነሻ ዋጋ 25% (አንድ አራተኛ) በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ሰነድ/ሲ.ፒ.ኦ በኦሮሚያ ባንክ ስም አሰርተው ይዘው መቅረብ አለባቸው።
የምዝገባ መጠናቀቂያ: የተጨራቾች ምዝገባ ከሐራጅ መዝግያ ሰዓት 5 ደቂቃ በፊት ይጠናቀቃል። ጨረታው ከፍተኛ ዋጋ የሰጠ ተጫራች እስኪለይ ድረስ ይቀጥላል።
የአሸናፊነት ማረጋገጫ: ከፍተኛ ዋጋ ያቀረበ ተጫራች ማሸነፉን የሚገልጽ ደብዳቤ ከባንኩ ህግ አገልግሎት ሲደርሰው ብቻ አሸናፊ ይባላል።
የቀሪ ክፍያ ጊዜ: አሸናፊው በጽሁፍ ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ ያሸነፈበትን ዋጋ በ15 ቀን ውስጥ ለባንኩ አጠቃሎ ገቢ ማድረግ አለበት።
በዚህ ጊዜ ውስጥ ካልከፈለ ያስያዘው ሲፒኦ ለባንኩ ገቢ ሆኖ ጨረታው ይሰረዛል፤ እንዲሁም ንብረቱ በድጋሚ ለሐራጅ ሲቀርብ ለሚፈጠረው ልዩነት ይጠየቃል።
የብድር ዕድል: የባንኩን ብድር ፖሊሲ መሰረት የሚፈለገውን ማስረጃ ላሟላ የጨረታ አሸናፊ ባንኩ ብድር ሊያመቻች ይችላል።
ተያያዥ ክፍያዎች: ጨረታውን ያሸነፈ ተጫራች ንብረቱን በማስተላለፍ ሂደት ለመንግስት የሚከፈሉ ክፍያዎችን (ግብር፣ የሊዝ ክፍያ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ፤ የስም ማዘወሪያ እና ማናቸዉም ወጪዎች) ይከፍላል።
ውዝፍ የሊዝ ክፍያ: ከእዳ ተመላሽ ብር ካለ ከተመላሽ ብር ላይ ይከፈላል፤ ተመላሽ ብር ከሌለ ግን የንብረቱ ጨረታ አሸናፊ ውዝፍ የሊዝ ክፍያን ሙሉ በሙሉ ይከፍላል።
ንብረት መጎብኘት: ተጨራቾች ለጨረታ የቀረቡትን ንብረቶች በስራ ሰዓት ፕሮግራም አስይዞ ለመጎብኘት ይችላሉ።
ተበዳሪው መገኘት: ባለዕዳዎቹ ባይገኙም ጨረታው ይካሄዳል።
ዋና መ/ቤት ሕግ አገልግሎት: 011 557 1372 እና/ወይም 0919 74 90 20
ለተራ ቁጥር 1 እና 2: ኦሮሚያ ባንክ መጋላ ቅርንጫፍ (025-113-10-23/24/25)
ለተ.ቁ.3 (የጠፋው ንብረት): ኦሮሚያ ባንክ ወሊሶ አካባቢ ቅርንጫፍ (011 3/41-26-53/41-27-30)
የባንኩ መብት: ባንኩ ጨረታውን በማንኛውም ጊዜ በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
No products in the cart.
Account details will be confirmed via email.
For faster login or register use your social account.