የመኖሪያ ቤት (G+2) የሐራጅ ጨረታ ማስታወቂያ – ወጋገን ባንክ
ወጋገን ባንክ አ.ማ በአዋጅ ቁጥር 97/90 እና 216/92 በተሰጠው ስልጣን መሰረት፣ ለሰጠው ብድር በዋስትና የተያዘን ዘመናዊ መኖሪያ ቤት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል።
1. የንብረቱ ዝርዝር መረጃ
-
የንብረቱ አይነት፦ ዘመናዊ መኖሪያ ቤት (G+2)
-
አድራሻ፦ አዲስ አበባ፣ የካ ክፍለ ከተማ
-
የቦታ ስፋት፦ 500 ካሬ ሜትር
-
የባለቤትነት ማረጋገጫ (ካርታ) ቁጥር፦ AA000051306364
-
የሐራጅ መነሻ ዋጋ፦ 30,627,626.14 ብር (ሰላሳ ሚሊዮን ስድስት መቶ ሃያ ሰባት ሺህ ስድስት መቶ ሃያ ስድስት ከ አስራ አራት ሳንቲም)
2. የሐራጅ ቀን እና ቦታ
-
የጨረታው ቀን፦ ሚያዝያ 13 ቀን 2018 ዓ.ም (April 21, 2026)
-
የምዝገባ ሰዓት፦ ከጧቱ 3፡00 – 4፡00 ሰዓት ድረስ ብቻ።
-
የጨረታው ሰዓት፦ ከጧቱ 3፡00 – 6፡00 ሰዓት።
-
ቦታ፦ ወጋገን ባንክ ዋና መስሪያ ቤት ህንፃ፣ 13ኛ ፎቅ በሚገኘው የመሰብሰቢያ አዳራሽ።
3. ተጫራቾች ማሟላት የሚገባቸው ቅድመ-ሁኔታዎች
-
የጨረታ ማስከበሪያ (CPO)፦ የጨረታውን መነሻ ዋጋ 1/4ኛ (አንድ አራተኛ) ማለትም በግምት 7,656,907 ብር በወጋገን ባንክ ስም ሲፒኦ (CPO) ማዘጋጀት።
-
የክፍያ ሁኔታ፦ አሸናፊው ቀሪውን ገንዘብ በ15 ቀናት ውስጥ መክፈል ይኖርበታል።
-
ልዩ እድል፦ ባንኩ መስፈርቱን ለሚያሟሉ አሸናፊዎች እንደ ድርጅቱ ፖሊሲ የብድር አገልግሎት ሊያመቻች ይችላል።
-
ተጨማሪ ክፍያዎች፦ ማንኛውንም ለመንግስት የሚከፈል ክፍያ (VAT ን ጨምሮ) አሸናፊው ይከፍላል።