የአዲስ አበባ የንግድ ማውጫ (Business Directory) የሕትመት ጨረታ
የአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት (AACCSA)
የአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት የ2026/27 የንግድ ማውጫ (Business Directory) በብቃት አሳትመው ማቅረብ የሚችሉ የህትመት ድርጅቶችን በድጋሚ በወጣ ግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል።
1. ተጫራቾች ማሟላት ያለባቸው መስፈርቶች
-
ሕጋዊ ሰነዶች፦ የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ የቫት (VAT) ምዝገባ፣ የግብር ክሊራንስ እና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN)።
-
የጨረታ ማስከበሪያ (CPO)፦ ብር 5,000.00 (አምስት ሺህ ብር) በሲፒኦ (CPO) ከቴክኒክ ሰነዱ ጋር ተያይዞ መቅረብ አለበት።
2. የጨረታ ሰነድ አወሳሰድ እና አቀራረብ
-
የሰነድ ዋጋ፦ የማይመለስ ብር 200.00 (ሁለት መቶ ብር)።
-
የሰነድ መገኛ፦ ሜክሲኮ አደባባይ፣ የንግድ ምክር ቤት ሕንፃ 1ኛ ፎቅ፣ ቢሮ ቁጥር 12።
-
አቀራረብ፦ ቴክኒካል እና ፋይናንሻል ፕሮፖዛሎች ለየብቻ በታሸገ እና ማህተም በተደረገበት ፖስታ መቅረብ አለባቸው።
-
የመዝጊያ ቀን፦ ሚያዝያ 5 ቀን 2018 ዓ.ም (April 13, 2026) ከቀኑ 8:00 (2:00 PM) ሰዓት።
-
የመክፈቻ ጊዜ፦ በዕለቱ ሚያዝያ 5 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8:30 (2:30 PM) ተጫራቾች ወይም ወኪሎቻቸው በተገኙበት።
3. አድራሻ እና መገናኛ