የፍሬድ ሆሎስ ፋውንዴሽን ኢትዮጵያ – የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር: FHFE /IFB/03/2026
ፍሬድ ሆሎስ ፋውንዴሽን ኢትዮጵያ በዘርፉ የተሰማሩ ብቁ ተጫራቾችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
1. ተጫራቾች ማሟላት ያለባቸው መስፈርቶች
ተጫራቾች የሚከተሉትን ሕጋዊ ሰነዶች ኮፒ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፦
-
በ2018 ዓ.ም. የታደሰ የንግድ ፈቃድ።
-
የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት።
-
የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN)።
-
የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ምዝገባ ሰርተፍኬት።
-
ከሚመለከተው አካል የተሰጠ የብቃት ማረጋገጫ ምስክር ወረቀት (CoC)።
2. የጨረታ ሰነድ አወሳሰድና አቀራረብ
-
የሰነድ አወሳሰድ፦ ተጫራቾች ሙሉ የጨረታ ሰነዱን 24 አካባቢ፣ ከገቢዎች ሚኒስቴር 200 ሜትር ገባ ብሎ በሚገኘው ባውዱች ሕንፃ (Bawdutch building) 1ኛ ፎቅ ላይ ከሚገኘው የድርጅቱ ቢሮ ማግኘት ይችላሉ።
-
አቀራረብ፦ የፋይናንስ (Financial) እና የቴክኒክ (Technical) ሰነዶች ለየብቻ በታሸገ ኤንቨሎፕ መቅረብ አለባቸው።
3. የጨረታ መዝጊያና መክፈቻ ጊዜ
-
የመዝጊያ ቀን፦ መጋቢት 23 ቀን 2018 ዓ.ም. (April 1, 2026) ከቀኑ 8፡00 ሰዓት።
-
የመክፈቻ ቀን፦ በዕለቱ መጋቢት 23 ቀን 2018 ዓ.ም. (April 1, 2026) ከቀኑ 8፡30 ሰዓት (ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት)።
-
ቦታ፦ ፍሬድ ሆሎስ ፋውንዴሽን ኢትዮጵያ ቢሮ፣ 24 አካባቢ፣ ባውዱች ሕንፃ 1ኛ ፎቅ።
4. አድራሻና የመገናኛ ስልኮች
ጠቃሚ ማሳሰቢያ፦ ተጫራቾች በጨረታ ሰነዱ ላይ የተጠቀሱትን መመሪያዎች በጥንቃቄ ማንበብና መሙላት ይኖርባቸዋል። ከመመሪያ 1 እስከ 6 የተጠቀሱትን ቅድመ ሁኔታዎች ያላሟላ ተጫራች ወዲያውኑ ውድቅ ይደረጋል። ድርጅቱ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።